About this episode
በምድር ላይ የመላእክት ዋናው ሥራቸው ወይም ተግባራቸው እግዚአብሄርን ማምለክና ማገልገል ነው፡፡ በሰማይ ያላቸው የተለምዶ ሥራቸውም እግዚአብሄርን ማመስገን ሲሆን በተለየና ባልተለመደ ሁኔታ ደግሞ ስናየው የእግዚአበሄርን ታሪካዊ የመዋጀትና የመታደግ ሥራውን ወደ ህዝቡ ዘንድ ማሳለጥ ነው፡፡ በመጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ ገና ከመጀመሪያው አካባቢ ጀምሮ የጌታ መላኣክ ወይም የእግዚአብሄር መልኣክ የሚሉ ሃሳቦች ከእግዚአብሄር ከራሱ ሥራና ተግባር ጋር የተያያዙ ናቸው፡፡