About this episode
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ፣ ግልጽ ያልሆነ ስውር ምስጢር ወይም በንግግር ደረጃ ብቻ ሊገለጽ የሚቻል ነገር ሳይሆን፣ በእውን የተደረገ አካላዊና ታሪካዊ ሀቅ ነው። ትንሣኤው በተግባር የተከናወነ፣ በበርካቶች በስፋት የተመሰከረ፣ ለብዙዎች ፊት ለፊት የታየና እውነት ስለ መሆኑ የተረጋገጠ ክሥተት ነው። የክርስቶስ ትንሣኤ ከታሪካዊ እውንነቱም በላይ፣ የርሱን መለኮታዊ ኀይል ከወቅታዊው ታሪካዊ ክሥተት ጋራ አቆራኝቶ የሚያሳይ ነው።