የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል#3 | አምስት ማጣፈጫዎች ክፍል 2

የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል#3 | አምስት ማጣፈጫዎች ክፍል 2

16:22 Aug 18, 2025
About this episode
በመጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ “ወንጌል” የሚለው ቃል ለየት ያለ ቃል ነው፡፡ ቃሉ አጭርና ውስን ቢመስልም በብዙ መንገዶች ሊገለጹ የሚችሉ ልዩ ልዩ ሃሳቦችንና መልእክቶችን የያዘ ቃል ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል፡- በመጀመሪያ ደረጃ በብሉይ ኪዳን ዋና እምብርት ላይ የተጠቀሱትን የድነትን ተስፋዎች ሁሉ አቅፎ በመያዝ ጉዳዩን በሚገባ ያብራራል፡፡ ቀጥሎ ደግሞ የናዝሬቱ ኢየሱስ በስሙ ለሚያምኑ ሁሉ ያዘጋጀውን መልካም ዜና ግልጽ አድርጎ ይነግረናል፡፡ እንዲሁም  ሰዎች ስለ ክርስቶስ የተነገረውን እውነት እና የእግዚአብሄርን የማዳን ሥራውን በሚገባ እንዲረዱ ለአድማጮች ሁሉ ግልጽ ያደርገዋል፡፡ በመጨረሻም፡- ይህ “ወንጌል” የሚለው ስም ራሱ በቀደመቺው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ልዩ ሥፍራ ተሰጥቶት የኢየሱስን ታሪክና ድንቅ ሥራዎቹን መናገር ብቻ ሳይሆን ለሚቀጥለውም ትውልድ ሊተላለፍ በሚችልበት ሁኔታ በአዲስ ኪዳናችን ውስጥ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ስለዚህ በመጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ “ወንጌል” የሚለው ቃል በተለየ ሁኔታና መልክ የምንረዳው ቃል ቢሆንም ለሁሉም ሰው ሊሆን በሚችል መልኩ በቀላሉ ሊገለጽ የሚችል የእግዚአብሄር መልእክት ነው፡፡ 
Select an episode
0:00 0:00